የአሜሪካ ሕግ አውጪዎች ትራምፕ ኢራንን እንዳያጠቁ የሚከለክለውን እርምጃ ውድቅ አደረጉ

የንባብ ጊዜ: 2 ደቂቃ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነት የመክፈት አቅማቸውን ለመገደብ በዴሞክራቶች የቀረበው ሃሳብ በተወካዮች ምክር ቤት ውድቅ ተደረገ። የአገሪቱ ሴኔት ተመሳሳይ ውሳኔ ከአንድ ቀን በፊት አስተላልፎ ነበር።

በ213 ለ 214 በሆነ ጠባብ ድምጽ ውድቅ የተደረገው የምክር ቤቱ የጦርነት ሥልጣን ውሳኔ ቢጸድቅም ፕሬዚዳንቱ ድምጽን በድምጽ በመሻር ሥልጣን ውድቅ የመደረግ ዕድሉ ከፍተኛ ነበር።

አብዛኛዎቹ ሪፐብሊካኖች በሁለቱም ምክር ቤቶች ውሳኔውን ተቃውመዋል። አንዳንድ ሕግ አውጪዎች ጦርነቱ ከዚህ ወር በላይ ከቀጠለ አቋማቸውን እንደገና ማጤን እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

ትራምፕ የግጭቱን ማብቂያ በተመለከተ የተለያየ የጊዜ ሰሌዳ ሲሰጡ የቆዩ ሲሆን በቅርቡ ጦርነቱ "ሊጠናቀቅ ተቃርቧል" ብለዋል።

ሐሙስ ዕለት በተካሄደው የምክር ቤት ድምጽ አሰሰጣጥ ላእ የኬንታኪው ተወካይ ቶማስ ማሳሲ ከዴሞክራቶች ጋር በመተባበር እርምጃውን የደገፉ ብቸኛው ሪፐብሊካን ሲሆኑ፣ የሜይኑ ጃሬድ ጎልደን ደግሞ ሃሳቡን የተቃወሙ ብቸኛው ዴሞክራት ሆነዋል።

በመጋቢት ወር የዴሞክራቶችን ጥረት የደገፉት የኦሃዮው ዋረን ዴቪድሰን በድምጸ ተአቅቦ አልፈዋል።

ሃሳቡን ያቀረቡት የኒውዮርኩ ዴሞክራት ግሪጎሪ ሚክስ ከድምጽ መስጫው በኋላ ለጋዜጠኞች እንደገለጹት ጎልደን እና ሌሎች እርምጃውን እንዲደግፉ እንደሚያበረታቱ ተናግረዋል።

ሚክስ ሌላ የጦርነት ውሳኔ እንደሚያስተዋውቁ ጠቁመዋል። ይህም በጦርነት ላይ የኮንግረሱን የበላይነት ለማፅደቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚቀጥሉ ዴሞክራቶች አመልክተዋል።

በባለፈው ወር ተመሳሳይ ውሳኔ ለማጽደቅ የተደረገው ሙከራ በጠባብ ድምጽ አልተሳካም። ሁለት ሪፐብሊካኖች ደግፈው ድምጻቸውን ሲሰጡ፤ አራት ዴሞክራቶች ደግሞ ተቃውመዋል።

ውሳኔው በምክር ቤቱን ቢጸድቅ እንኳን በሴኔት ውስጥ ከባድ ፈተና ይገጥመዋል። ትናንት ተመሳሳይ ውሳኔ በሴኔቱ ቀርቦ 47 ለ 52 በሆነ ድምጽ ውድቅ ተደርጓል። ሁለቱንም ምክር ቤቶች ለማለፍ ቢችል እንኳን ከትራምፕ ድምጽን በድምጽ የመሻር ስልጣን አይተርፍም።

አንዳንድ ሪፐብሊካኖች ግጭቱ እየሰፋ ከሄደ ወይም ከቀጠለ ለውሳኔው ያላቸው ተቃውሞ ሊለወጥ እንደሚችል ጠቁመዋል።

በፌዴራል ሕግ መሠረት ወታደራዊ እርምጃዎችን ከ60 ቀናት በላይ ለማስቀጠል የኮንግረሱን ፈቃድ ይጠይቃል። የአሜሪካ-እስራኤል ጥቃት የተጀመረው የካቲት 21 ነበር።