ትራምፕ በኢራን ላይ ዳግም ጥቃት ለመክፈት እያጤኑ መሆኑን ዎል ስትሪት ጆርናል ዘገበ
አሜሪካ እና ኢራን በፓኪስታን ያካሄዱት ድርድር ሳይሳካ መቅረቱን ተከትሎ ትራምፕ ቴህራን ላይ ዳግም ጥቃት የመክፈት ሃሳብ እንዳላቸው ዎል ስትሪት ጆርናል ዘገበ።
ዎል ስትሪት ጆርናል ስማቸውን ያልገለጻቸው የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ከሌሎች እርምጃዎች በተጨማሪ ኢራን ላይ ድብደባ ለመጀመር እያጤኑ መሆኑን ዘግቧል፥።
ትራምፕ እሁድ ዕለት የባሕር ኃይላቸው የሆርሙዝ ወሽመጥን እንዲዘጋ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
ዋይት ሐውስ ቢቢሲ ስለ ጋዜጣው ዘገባ ላቀረበው ጥያቄ ሁሉም አማራጮች ጠረጴዛ ላይ ናቸው ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ኦሊቪያ ዌልስ “ፕሬዚዳንቱ የሆርሙዝ ወሽመጥን እንዲዘጋ ባሕር ኃይሉን አዝዘዋል። የኢራንን ዝርፊያ ያበቃል እና ሁሉንም ተጨማሪ አማራጮች በጠረጴዛው ላይ ተቀምጠዋል። ለዎል ስትሪት ጆርናል ፕሬዚዳንቱ ቀጥሎ የሚያደርጉትን መረጃውን የሰጠ ማንኛውም ሰው በግልጽ ግምቱን ነው ያስቀመጠው” ብለዋል።